በሀገራችን ለመጣው ፖለቲካዊ ለውጥ ዋና ተዋንያን ህዝብ ሆኖ፤ ወጣቶች የአንበሳውን ድርሻ ይጋራሉ፡፡ ፍትሃዊ ተሳትፎና ተጠቃሚነት፣ ዲሞክራሲ፣ ነፃነትና እኩልነት በሀገራችን ለተመዘገበው ለውጥ ገፊ የትግል ማዕዘኖች ናቸው፡፡
ለውጡ ገና በዳዴ የሚድህ ቢሆንም በተፈለገው ፍጥነት መሔድ እንዳይችል በውስጥና በውጪ አርበኞች የሚገጥመው ፈተናም ቀላል ተደርጎ የሚወሰድም አይደለም፤ ወጣቶች ህይወታቸውን የሰጡለት ሀገራዊ ለውጥ እንዲያረጋግጥላቸው የሚፈልጉት ተሳትፎና ተጠቃሚነት እንዲመጣ ቀጣይነት ያለው "በአመክንዮ የታገዘ ሞጋችነት" አማራጭ የሌለው ምርጫ ተደርጎ ይወሰዳል፡፡
የወጣቶችን ትዕግስት የሚፈታተኑ እዚህም እዛም ተጠራቅመው የቆዩና የታፈኑ በርከትከት ያሉ ጥያቄዎች መኖራቸው የማይካድ ሀቅ ቢሆንም፤ በነበራቸው የመሪነት "Statuesque" ያወረሱንን ጥያቄዎች በመኮርኮር ወጣቶችን የሁከት ዋና ተዋንያን ለማድረግ በጥፋት ሀይሉ ቢሞከረም "ለአይጧ ተብሎ ምጣድ እንደ ማይሰበር" በቂ ምላሽ አግኝተዋል፡፡
የሆነው ሆኖ "ለውጡን ጭራ ይዘናል ከያዝንም አንለቅም" ለውጡ ላይ የሚታየውን ጉድለት በማረም የዛሬዋና የነገዋ ኢትዮጵያ ለወጣቶች ጥያቄ ምላሽ መስጠት የምትችል ሀገር እንትሆን በምክንያት እንተጋለን፤ የወጣትነት ዘመናችንን ለመልካም ነገሮች ሁሉ ግባታ በማዋል ችግሮችን ተጋፍጠን ኢትዮጵያን እናንፃለን፡፡